ባንካችን ከሀገር ውጭ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን ማዕከል ያደረጉ የባንክ አገልግሎቶችን ለአውደ ርዕይው ተሳታፊዎች አስተዋውቋል።
በእስካይላይት ሆቴል በተዘጋጀው አውደ ርዕይ ላይ የብሔራዊ ባንክ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ ፣ የባንካችን ዋና አስፈፃሚ አቶ ተፈሪ መኰንን ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖን ጨምሮ የበርካታ ባንኮች ከፍተኛ ዓመራሮች እንዲሁም በውጭ ሀገር የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ተሳትፈዋል።
ኦሮሚያ ባንክ ዜጎቻችን ከባህር ማዶ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ከእኛ ጋር በሚሰሩ ገንዘብ አስተላላፊ ወኪሎች በኩል የሚልኩትን የውጭ ሀገር ገንዘብ በታማኝነት በማድረስ መልካም ስም አፍርቷል።
በተጨማሪም ባንኩ የዲያስፓራውን ማህበረሰብ በልዩነት ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ የባንክ አገልግሎቶች ቀርፆ ተግባራዊ እያደረገ ነው።