ከተለያዩ የብረታ ብረት ምርቶች የተሰራዉ ባለ ግርማ ሞገሱን የፈረስ አርማ መርቀዉ የከፈቱት የባንካችን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተፈሪ መኮንን፤ ይህ የጥበብ ስራ የባንካችንን አርማ በልዩ ሁኔታ ከማስተዋወቅ በተጨማሪ፤ ለመዲናችን የኮሪደር ልማት ተጨማሪ ዉበት ፈጥሯል ብለዋል፡፡
የቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ስራ አስፈፃሚ አቶ አበራ አለሙ በበኩላቸው ቦሌ መንገድ የሀገር ዉስጥ እና የዉጭ ሀገር እንግዶች እና ጎብኚዎች በብዛት የሚመላለሱበት ስለሆነ፤ ኦሮሚያ ባንክ ከኮሪደር ልማቱ ጋር የተጣጣመ፣ ከተማችንን የሚመጥን እና ጥራቱን የጠበቀ የእንግዶች የአይን ማረፊያ ቀርፅ በመስራቱ ኩራት ይሰማናል ብለዋል።
ቦሌ መንገድ ላይ በሚገኘዉ የባንካችን ዋና መስሪያ ቤት ጎን የቆመዉ አና በሁለት እግሮቹ ከፍ ብሎ የሚታየዉ ባለ ግርማ ሞገስ የፈረስ ቅርፅ 4 ሜትር ተኩል ርዝማኔ ያለዉ ሲሆን ከ700 ኪሎ ግራም በላይ ይመዝናል፡፡