Get In Touch
Bole, Africa Avenue Addis Ababa Ethiopia
Email info@orointbank.com
Ph: + 251 115 572 002
P.O.Box: 27530/1000 Addis Ababa,Ethiopia
Fax: + 251 115 572 002
SWIFT CODE: ORIRETAA

የኦሮሚያ ባንክ 7ኛዉ ዓመታዊ የችግኝ ተከላ መርኀ-ግብር ተካሄደ

የኦሮሚያ ባንክ 7ኛዉ ዓመታዊ የችግኝ ተከላ መርኀ-ግብር ገላን ክ/ከተማ በሚገኘዉ በባንኩ የልህቀት እና ኮንቬንሽን ማዕከል ተካሄደ፡፡

በዚህ የችግኝ ተከላ መርኀ- ግብር ላይ የባንኩ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችን፣ የፊንፊኔ ከተማ ቀጠና ጽ/ቤት ዳይሬክተሮች እና የቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆችን ጨምሮ የገላን ክ/ከተማ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

የኦሮሚያ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኦቦ ተፈሪ መኮንን ባስተላፉት መልዕክት ባንካችን ላለፉት 7 ዓመታት ሰራተኞቹን በማሳተፍ በችግኝ ተከላ መርኃ- ግብር ላይ በስፋት ሲሳተፍ መቆየቱን አስታዉሰዉ በቀጣይም ባንኩ በሀገራዊ ጉዳች ላይ በንቃት መሳተፉን ይቀጥላል ብለዋል፡፡

በዚህ የችግኝ ተከላ መርኃ-ግብር የተሳተፊ የኦሮሚያ ባንክ የስራ ዓመራር አባላት እና የገላን ክፍለ ከተማ የስራ ሀላፊዎች በባንኩ እየተገነባ ያለዉን የልህቀት እና የኮንቬንሽን ማዕከል ሁለተኛዉን ምዕራፍ ግንባታ ጎብኝቷል፡፡